Shiro Meda, In front of America Embassy,
Addis Ababa, Ethiopia
+251-11-123-22-30/+251-11-123-61-30
Toll free number "9799"
General Info: info@eta.et
eta.gov.et@gmail.com
IT:hemis.info@gmail.com
ባለሥልጣኑ በፍቼ ከተማ የአረንጓዴ አሻራና የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተከናወነ
==>የ5 አቅመ-ደካሞች ቤት እድሳት ተከናውኗል፤
==>ለ250 ችግርተኛ ተማሪዎች የደብተር፣ የስክሪፕቶ እና የመማሪያ ቅሳቁስ መያዣ ቦርሳ ተበርክቷል፤
======= #WMCC=========
የኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን አመራሮችና ሰራተኞች በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በፍቼ ከተማ አስተዳደር አበበች ጎበና ተብሎ በሚጠራው የመታሰቢያ ቦታ በመገኘት “አረንጓዴ አሻራችን ለትውልዳችን!” በሚል መሪ-ቃል ችግኝ በመትከል የአረንጓዴ አሻራ እና የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ ግብር አከናውነዋል።
ከአረንጓዴ አሻራው መርሃ-ግብሩ በተጨማሪ ለአምስት አቅመ ድካሞችን ቤት እድሳት የሚውል ቆርቆሮ ገዝቶ ማቅረብን ጨምሮ የቤት እድሳቱን የማስጀመር ስራ ተከናውኗል፤ እንዲሁም ለ250 ተማሪዎች ከ200 ሺ ብር በላይ የሚገመት የደብተር፣ የስክሪፕቶ፣እና የመማሪያ ቁሳቁስ መያዣ ቦርሳ የማበርከት ድጋፍ ተደርጓል።
በመርሃ-ግብሩ የባለሥልጣኑ አመራሮችና ሰራተኞች፣ የፍቼ ከተማ ከንቲባ አቶ ክፍሉ ከበደ፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
ሐምሌ 28 ቀን 2014 ዓ.ም